ምስጋና
------------
ለኤርትራው ፕሬዝዳንት ጉብኝት ስኬታማነት የባለድረሻ አካላት ላደረጉት አስተዋፅኦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ምስጋናውን ይገልፃል፡፡
የኤርትራ ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ኢሳያስ አፈወርቂ በአገራችን ያካሄዱትን ስኬታማና የሁለቱን አገሮች ህዝቦች ያስተሳሰረ ይፋዊ የስራ ጉብኝት አጠናቀው ዛሬ ወደ አስመራ ተመልሰዋል፡፡
ወደ አገራቸው ከመመለሳቸው በፊት በኢትዮጵያና የኤርትራ ኤምባሲን ከክቡር የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ጋር መርቀው ከፍተዋል፡፡
መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በተለይም የአዲስ አበባ፣ ሃዋሳ እና የአከባቢዎቹ ነዋሪዎች ልዑካኑ ላደረጉት ደማቅና ወንድማዊ አቀባበልና አሸኛኘት፤ ሁሌም የምንኮራና የምንተማመንባቸው የፀጥታ ኃይሎችና አመራሮቻቸው ለጉብኝቱ ስኬት ጉልህ ሚና ሰለነበራቸው ምስጋናችን ከፍተኛ ነው፡፡
መላው የውጭ ጉዳይ ሠራተኞች ጉብኝቱ በታቀደለት መልኩ እንዲከናወን በአጠቃላይም ከኤርትራ ጋር አዲስ የትብብር ዲፕሎማሲ እንዲኖር በትጋት በመስራታቹ የታሰበው ሁሉ የተሳካ ሆኗል እና እንኳን ደስ አላቹሁ ከልብ ምስጋዬን አቀርባሉሁ፡፡
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ስራ አስኪያጅ አቶ ረሻድ ከማልና የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሙሉስልጣን ስራ አስኪያጅ አቶ ሃብታሙ ተገኝ የኤርትራ ኤምባሲ በሁለት ቀናት ውስጥ ተጠግኖ እና ተስተካክሎ ለምረቃ እንዲበቃ በማድረግ ጉብኝቱ የበለጠ ፍሬያማ እንዲሆን አድርገዋል፡፡
በአጠቃላይ ከኤርትራ ጋር አዲስ የትብብር እና የሰላም ሂደት ዕውን እንዲሆን አስተዋፅኦ ያደረጋቹ ወገኖቻችን ላቅ ያለ ምስጋናችን ይደረሳቹ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ