Dehai News

(ኢቢሲ) የኢትዮ-ኤርትራ ሰላም መፈጠር ለአገር መከላከያ ሰራዊት ፋይዳ የጎላ ሆኖ ማገኘቱን የሰሜን ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች ተናገሩ፡፡

Posted by: Semere Asmelash

Date: Thursday, 07 February 2019

Feb 6 ፣2019

የኢትዮ-ኤርትራ ሰላም መፈጠር ለአገር መከላከያ ሰራዊት ፋይዳ የጎላ ሆኖ ማገኘቱን  የሰሜን ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች ተናገሩ፡፡

“ህገ መግስታዊ ታማኘነታችንና ህዝባዊ ባህሪያችንን ጠብቀን የተጀመረው ለውጥ እናስቀጥል” በሚል እየተከበረ ያለው 7ኛው የሰራዊት ቀን በዕዝ ደረጃ ባድመ አካባቢ ለሚደረገው የማጠቃለያ ስነ ስርዓት በተመለከተ አመራሮቹ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

የሰሜን ዕዝ የሎጂስቲክስ ዘርፍ ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ከድር አራርሳ የኢትዮ-ኤርትራ ሰላም መፈጠር  ህዝቡ ሰላማዊ እንቅስቃሴ  እንዲፈጠር ከማድረጉ በተጨማሪ ሰራዊቱን  ለማሰልጠንና  ያለስጋት  ስራዎቹን እንዲያከናውን ያግዛል ብለዋል፡፡

በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ የተጀመረው የማሻሸያ ስራ በተቋም ደረጃ  ከላይ እስከ ታች  እየሰፋና እየተጠናከረ  መሆኑን ተናግርዋል፡፡ሰራዊቱ ኃይሉን እያጠናከረና  የብሄር ተዋፅኦውን ይበልጥ እያስተካከለ እንደሚገኝም  ምክትል አዛዡ አስረድተዋል፡፡

የሰሜን ዕዝ የሰው ሀብት አመራር ዘርፍ ምክትል አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ገ/እግዚያብሄር በየነ 7ኛው የሰራዊቱ ቀን ከስጋት ነፃ በሆነና የሁለቱም አገራት ወታደሮች ከምሽግ ወጥተው በጋራ መዋል በጀመሩበት የሚከበር በመሆ ልዩ ያደርገዋል ብለዋል፡፡

በዓሉ ሰራዊቱ ከለውጥ በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ እየተከበረ ያለ በመሆኑ  ሰራዊቱ ቃል ኪዳኑን የሚያድስበት አጋጣሚ አድርጎ እንደሚጠቀምበትም ተናግረዋል፡፡

እስካሁን በተለያዩ ዝግጅቶች የተከበረ ያለው የሰራዊቱ ቀን የማጠቃያ ስነ ስርዕቱን ባድመ ላይ ይካሄዳል፡፡

በበዓሉ ሰራዊቱ ዝግጅቱን  የሚያሳዩ የተለያዩ ወታደራዊ ትዕይንቶችና የፓናል ውይይት የሚደረግ ሲሆን  ሰራዊቱን ያገለገሉ አባላት የክብር አሸኛኘት ይደረግላቸዋል ተብሏል፡፡የትግራይ ክልልና አጎራባች ክልሎች ተወካዮች በበዓሉ አከባበር ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በሙሉጌታ ተስፋይ



EmbassyMedia - ራብዓይ ግንባር!

Dehai Events