World News

DW.com: የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ግሽበት በኢትዮጵያ

Posted by: Berhane Habtemariam

Date: Sunday, 19 March 2017

የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ግሽበት በኢትዮጵያ

በቅርቡ በተለይ ለመንግሥት ሠራተኞች የደሞዝ ማስተካከያ መደረጉ ፣ ሐገሪቱን በከፊል የመታው ድርቅ  እና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች የሁዳዴ ጾም መግባቱ  በመሠረታዊ ሸቀጦች  አትክልት እና ፍራፍሬዎች ላይ ለታየው የዋጋ ጭማሪ እንደ ምክንያት የሚጠቅሱ አሉ ።

March 19, 2017

 
 

ራድዮ፡ የኑሮ ውድነት በኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ በቅርብ ጊዜያት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ እጅግ መናር ህብረተሰቡን ማማረሩ ቀጥሏል ። በቅርቡ በተለይ ለመንግሥት ሠራተኞች የደሞዝ ማስተካከያ መደረጉ ፣ ሐገሪቱን በከፊል የመታው ድርቅ  እና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች የሁዳዴ ጾም መግባቱ  በመሠረታዊ ሸቀጦች  አትክልት እና ፍራፍሬዎች ላይ ለታየው የዋጋ ጭማሪ እንደ ምክንያት የሚጠቅሱ አሉ ። የአቅርቦት ችግር እና ባለፈው ዓመት መጨረሻ እና በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ የተካሄደው ተቃውሞም  ለችግሩ አስተዋጽኦ አድርጓልም ይባላል ። መንግሥት በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች አካሄድኩ ባለው የዳሰሳ ጥናት በመሠረታዊ ሸቀጦች እና በአትክልት እና ፍራፍሬዎች ላይ የተደረገውን ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ምክንያታዊ አይደለም ይላል ። የኢትዮጵያ ንግድ ሚኒስቴር ባለፈው ሳምንት እንዳስታወቀው ከችግሩ መንስኤዎች መካከል ሰው ሰራሽ እጥረቶች ይገኙበታል ። በዚህ አግባብ ባልሆነ መንገድ ለማትረፍ በሚሞክሩ ነጋዴዎች ላይም  እርምጃዎችን እንደሚወስድም አስታውቋል ። ይሁን እና የዋጋ ግሽበት ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ሠሞን ብቻ የሚከሠት አይደለም ። ሥኳርን የመሳሰሉ ሸቀጦችን ጨርሶ ከገበያ እስከ መጥፋት ያደረሰው የደሞዝ ጭማሪ ከመደረጉ እና ፣ ድርቅም ሆነ ፆም ከመግባቱ በፊት ነው ።ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚያሻቅበውን የሸቀጦች ዋጋ ትርፍ ለማጋበስ የሚሹ ወገኖች የፈጠሩት ነው ማለትም ብዙዎችን የሚያሳምን ምክንያት አይደለም ። በኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት መንስኤዎች እና መፍትሄዎቹ የዛሬው እንወያያው መነጋገሪያ ርዕስ ነው ። በዚህ ላይ የሚወያዩ ሦስት እንግዶች ጋብዘናል እነርሱም፤ አቶ አዲሱ ተክሌ የኢትዮጵያ ንግድ እና የዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት አማካሪ ፣ አቶ ገብረ መድህን ቢረጋ የኢትዮጵያ ሸማቾች መብት ጥበቃ ማህበር ፕሬዝዳንት አቶ ሙሼ ሰሙ የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ኢዴፓ የቀድሞ ዋና ፀሐፊ እና የባንክ ባለሞያ ናቸው ። የኢትዮጵያ ንግድ ሚኒስቴር ሃላፊዎች በውይይቱ ላይ እንዲሳተፉ በመስሪያ ቤቱ ህዝብ ግንኙነት በኩል ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም ።ሙሉውን ውይይት የድምፅ ማዕቀፉን በመጫን ማድመጥ ይችላሉ ። 

ኂሩት መለሰ

ልደት አበበ

Audios and videos on the topic


6ይ ክፋል: ማዕበል ስርሒት ፈንቅል - የካቲት 1990 - ሰነዳዊት ፊልም| sirihit fenkil 1990 - part 6 - ERi-TV Documentary

Dehai Events