Date: Saturday, 13 May 2017
ቢቢኤን ሬድዮ
May 13, 2017 |
Video: https://www.youtube.com/watch?time_continue=440&v=8taoyHggxGI
በሰራዊቱ ላይ እምነት ያጣዉ ህወሃት መራሹ መንግስት አዳዲስ ወጣቶችን ሰራዊቱ ዉስጥ ለማስገባት ምልመላዉን አጧጥፎ ቀጥሏል።ዘመናዊ የጦር መሳሪያዎች በትግራይ ተወላጆች ቁጥጥር ብቻ እንዲዉሉ የተደረገ ሲሆን ይህንኑ ከግብ ለማድረስ የተመረጡ የትግራይ ወጣቶች ከፍተኛ ብቃት ባላቸዉ አሰልጣኖች እየሰለጠኑ መሆኑን የሰራዊቱ አባላቶች ያስረዳሉ። የማትሪክ ዉጤት በተማሪዎች ላይ ሆን ተብሎ እንዲበላሽ የማድረግ ሴራ እንዳለ የሚያስረዱት የሰራዊቱ አባላት ወጣቶችን በከፍተኛ ደሞዝ አታሎ ለማስገባት መልማይና አታላይ የደህንነት ግብረሃይል በየክልሉ መሬት መሰማራቱንም ያጋልጻሉ።