World News

(አብመድ) የኤርትራ ልዑክ የጥምቀት በዓልን ለመታደም ጎንደር ገባ፡፡

Posted by: Semere Asmelash

Date: Sunday, 19 January 2020

የኤርትራ ልዑክ የጥምቀት በዓልን ለመታደም ጎንደር ገባ፡፡



ባሕር ዳር (አብመድ) በኢትዮጵያ የኤርትራ አምባሳደር የተመራ ልዑኩ ጎንደር አፄ ቴዎድሮስ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ በከተማው ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ማስተዋል ስዩም (ኢንጂነር) እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል ተደርጎለታል፡፡

ከኤርትራ ተጨማሪ ልዑካን ወደ ጎንደር እንደሚገቡም እየተጠበቀ ነው፡፡

የውጭ ሀገራት እና የሀገር ውስጥ እንግዶችም ወደ ከተማዋ የገቡ ነው፡፡

እንግዶችን ለመቀበል ደግሞ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና ፋሲል ከነማን ጨምሮ የከተማዋ ባለሀብቶችና ተቋማት ለመጓጓዣ አገልግሎት መኪኖችን በማቅረብ ላይ ናቸው።

ዘጋቢ፡- ድልነሳ መንግሥቴ
Afbeelding kan het volgende bevatten: 10 mensen, staande mensen, pak, bruiloft en buiten
Afbeelding kan het volgende bevatten: 1 persoon, binnen
Afbeelding kan het volgende bevatten: 4 mensen, zittende mensen, woonkamer, tafel en binnen
Afbeelding kan het volgende bevatten: 3 mensen, lachende mensen, zittende mensen en binnen



EmbassyMedia - ራብዓይ ግንባር!

Dehai Events