Date: Monday, 04 May 2020
አዲስ አበባ፣ (ኤፍ.ቢ.ሲ) ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከኤርትራው ከፕሬዚደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ተገናኙ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ በፌስቡክ ገፃቸው ባወጣት መረጃ “ፕሬዚደንት ኢሳይያስ አፈወርቂን እንኳን ወደ ኢትዮጵያ በድጋሚ መጡ ለማለት እወዳለሁ” ብለዋል።
“ለሁለት ቀናት በሚያደርጉት ቆይታ፣ በሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት እናደርጋለን፤ የዓለም አቀፋ ማኅበረሰብ አካል በመሆናችን ስለ ተጋፈጥናቸው ፈታኝ ሁኔታዎች እንወያይባቸዋለን” ሲሉም ገልፀዋል።