Dehai News

ኢትዮጵያ ምእንቲ ቀይሕ ባሕሪ ኢላ ንኤርትራ ክትወርር ሓሳብ የብላን – ቀዳማይ ሚኒስተር ኣብይ ኣሕመድ

Posted by: Semere Asmelash

Date: Thursday, 20 March 2025


ቅድሚ 3 ሰዓታት

ኢትዮጵያ ለቀይ ባህር ስትል ኤርትራን የመውረር ፍላጎት የላትም – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)


On Mar 20, 2025  

አዲስ አበባ፣ (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ለቀይ ባህር ስትል ኤርትራን የመውረር ፍላጎት እንደሌላት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የኢትዮጵያ ፍላጎት እንነጋገር፣ ሰጥቶ በመቀበል መርህ፣ ህዝቦች በሚጠቀሙበት መርህ እንወያይ የሚል ነው ብለዋል።

የኤርትራ ህዝብ የሚያስፈልገው ልማት ነው፣ ተባብረን መልማትና መስራት እንጂ አንዱ አንዱን መውጋት የእኛ እቅድ አይደለም ነው ያሉት፡፡

ኢትዮጵያ ላይ ማንም ሀገር ወረራ ሊፈጽም እና ከጀመርነው ህልም ሊያስቆመን ይችላል የሚል ስጋት የለብንም ብለዋል፡፡

በቂ ዝግጅት ስላለን ማንም አያስቆመንም፣ ዝግጅት የምናደርገውም ጦርነትን ለማስቆም ነው ሲሉ አክለዋል፡፡

የባህር በር ጥያቄን ማንሳት ነውርነቱ አቁሟል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)÷ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አቋምም በዓለም ላይ ትልቅ ሀገር ሆኖ የባህር በር የሌለው የለም ስለሆነም በሰጥቶ መቀበል መርህ ሊሆን ይገባል የሚል መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ አጀንዳ ለመስጠት የመጣ ሳይሆን ባለፉት ዓመታት ትኩረት የተሰጠው እና በመደመር መጽሐፍ ላይ የተካተተም ነው ብለዋል፡፡

በብርሃኑ አበራ



ፈንቅል - 1ይ ክፋል | Fenkil (Part 1) - ERi-TV Documentary

Dehai Events