Date: Thursday, 06 November 2025
ግልጽ ደብዳቤ
ለክቡር ዶ/ር አብይ አህመድ
ጠቅላይ ሚኒስትር
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
የቀይ ባህር ሰው
ዋሽንግተን ዲ ሲ
ጥቅምት 15 2025
ጉዳዩ፡ በኤርትራ ሉዓላዊነት ፥ የግዛት አንድነት እና ህዝቧ ላይ ያነጣጠሩ መልእክቶችህ
በቅድሚይ ኤርትራዊ ባህላችን በሚጠይቀው ጨዋነት የአክብሮይ ሰላምታየን አስቀድማለሁ። ቀጥሎም በኤርትራ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ላይ ያነጣጠሩ መልዕክቶችህ በሁለቱ ወንድማማች ህዝቦች መካካል ጥላቻን የሚያራግቡና ለጦርነት የሚቀሰቅሱ ሃላፊነት የጎደላቸው ናቸው። የዚህ ግልጽ ደብዳቤ አላማ በቂ ማስረጃ በማቅረብ የሃሰት ትርቶችህን ማጋለጥና የኢትዮጵያ ህዝብ ትክክለኛ ግንዛቤ ላማስጨበጥ ይረዳል በሚል ተስፋ ነው።
1. "የአለም አቀፍ ህግ የኢትዮጵያን
የባህር በር ባለቤነት እውቅና ይሰጣል፡"የባህር ኃይል ያቋቋምነው የባህር በር ባለቤትነት ለመሆን ነው"
የአለም-አቀፍ ህግ ወደብ የሌላቸው አገሮች ወደብ ካላችው አገሮች ጋር በመስማማት በወደብ የመጠቀም መብት እንዳላቸው በግልጽ ያስቀምጣል፡፡ የባህር መውጫ ማግኘት መብት ሲባል ግን በሃይል የመያዝ ወይ በባለቤትነት መያዝ ሳይሆን በወደቦቹ መጠቀም (access to the sea) መብት ብቻ መሆኑን በማያሻማ ቃላት ተደንግጓል። የባህር በር ያላቸው አገራት የባህር በር የሌላቸውን ጎረቤት አግሮችን ማስተናገድና የልማት አጋር ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው እውቅና ይሰጣል። ይህ የሚፈጸመውም በአለም አቀፍ ህግ፡ ሉአላዊነትን የማክበር መርህ ላይ የተመስረት ሲሆን ብቻ መሆኑን አስምሮበታል።
በአለም ዙርያ 44 አገሮች (700 ሚልዮን የህዝብ ብዛት ያላችው) የባህር በር ባላቤቶች አይደሉም። ከነዚሁም 16ቱ አገሮች (36%) በአፍሪካ የሚገኙ ሲሆን ኢትዮጵያን ሳይጨምር 15ቱ 365 ሚልዮን የህዝብ ብዛት ያላቸው ናቸው። እነዚህ አገሮች ያደረጉት የአለም አቀፍ ህግ በሚፈቅደው መሰረት፥ ከጎረቤት አገሮች ጋር ባደረጉት ስምምነት የባህር በር መውጫና መተላለፍያ መብታቸውን አስከብረው የህዝባቸውን ኑሮ ለማሽሽል በመረባረብ ላይ ይገኛሉ። በተመሳሳይ ኢትዮጵያና ኤርትራ በአለም አቀፍ ህጎች መሰረት ሁለቱንም ተጥቃሚ የሚያደርግ የወደብ አጠቃቀም ስምምነት ማድረግ ይችላሉ።
2. "ከተቻለ በሰላማዊ መንገድ ካልሆነ ግን በጦርነት ኢትዮጵያ የወደብ ባላቤትነትዋን ታረጋግጣለች"፡
"የህዳሴውን ግድብ ጨርሰናል፥ አሁን የቀረው የቀይ ባህር ጉዳይ ነው"
የአለም-አቀፍ ስርዓት የተመሰረተው ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ማክበር መርህ (Principle of Respect for Sovereignty and Territorial Integrity) ላይ ነው። የአገር ሉዓላዊነት መሰረታዊ መርህ ወደብ ባለቤት አገሮች ብቸኛ እና ፍፁም የሆነ የባለቤትነት መብትን ይሰጣል። በተጨማሪ የተ/መ ቻርተር አንቀጽ 2 (4) በሌላ አገር ሉዓላዊነት እና ግዛታዊ አንድነት ላይ ሃይል መጠቀም ወይ ማስፈራራት አይፈቅድም።